አዋሽ ባንክና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በቀጣይ ጊዜያት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

የመግባብያ ስምምነቱ ዋና አላማ የደንበኞቹን ፍላጎት ለማርካትና ዘመኑን የዋጁ ቀልጣፋ የባንክ አገልግሎቶችን ለህብረተሰቡ በመስጠት ላይ የሚገኘው አዋሽ ባንክ አዳዲስ የባንኪንግ ቴክኖሎጂዎችን በሃገሪቱ አንጋፋ እና በስርጭት ሽፋኑ ግንባር ቀደም የመንግስት የሚዲያ ተቋም ከሆነው ኢቢሲ ጋር በጋራ በመስራት በሰፊው ለማስተዋወቅና እየሰጠ በሚገኘው የባንኪንግ አገልግሎቶች ላይ በቂ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው፡፡
በመሆኑ የመግባቢያ ስምምነቱ ለሁለቱ ተቋማት ለአገራችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ለውጥ አብረውና ተደጋግፈው ለመስራት ምቹ መደላድልን የሚፈጥር ነው፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ስምምነቱ የባንኩ አገልግሎቶች በየጊዜው ለህብረተሰቡ እንዲደርሱና ህብረተሰቡም የአገልግሎቶቹ ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻል ነው፡፡ እንደዚሁም ኢቢሲ አገልግሎቱን ለማዘመንና ተደራሽነቱን ለማስፋፋት የሚያደርገውን ጥረት ባንኩ በሚችለው አቅም ሁሉ እንዲያግዘው ይረዳል፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱ የተፈረመው በአዋሽ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ በአቶ ፀሐይ ሽፈራው እና በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ በ ዶ/ር ንጉሴ ምትኩ ታህሳስ 19 ቀን 2012 ዓ.ም በረመዳ ሆቴል ነበር::

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Apr 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.8795 58.0171
GBP
67.5577 68.9089
EUR
60.7928 62.0087
AED
14.0132 14.2935
SAR
13.7240 13.9985
CHF
59.3920 60.5798

Exchange Rate
Close