አዋሽ ባንክ የካቲት 12 ቀን 2012 ዓ.ም የደቡብ ምዕራብ የአገራችን ክፍል ፈርጥ በሆነችውና በንግድ መዳረሻነቷ በምትታወቀው ጥንታዊቷ የጅማ ከተማ ‘ሂራ’ ተብሎ የተሰየመውን የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት አድረጓል፡

በመላው የአገሪቱ ክፍሎች ለደንበኞቹ ቀልጣፋ፣ የተሟላና ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በመስጠት የሚታወቀው ባንካችን አገልግሎቱን በተሻለ ደረጃ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን እስከ ዛሬ ድረስ በሁሉም ቅርንጫፎች በመስኮት ደረጃ ይሰጥ የነበረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልገሎትን አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን በመክፈት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሠረት ይህን ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ኢክኽላስ ብሎ በመሰየም (ብራንድ በማድረግ) እንቅስቃሴ የጀመረ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ አራት ቅርንጫፎችን በአዲስ አበባ ከተማ በመክፈት የተሟላ የባንክ አገለግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ እንደዚሁም በምስራቁ የአገራችን ክፍልም በምስራቅ ሐረርጌ ዞን መልካ ራፉ ከተማ እና በኢትዮጵያ ሱማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን ከፍቶ ለአገልገሎት አብቅቷል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Mar 29, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.6236 57.7561
GBP
68.3299 69.6965
EUR
61.1818 62.4054
AED
13.9527 14.2318
SAR
13.6630 13.9363
CHF
59.8379 61.0347

Exchange Rate
Close