አዋሽ ባንክ ከኮሮና ወረርሽኝ ጋር ተያይዞ ሊያጋጥም የሚችለውን የንግድ ሂደት መስተጓጎል ከግምት በማስገባት የሚከተሉትን የአገልግሎት ክፍያ ማሻሻያዎችን አድርጓል፡፡
1. ከውጪ አገር ምርቶችን የሚያስገቡ ደንበኞቻችን ለኤልሲ ማራዘሚያ ይከፍሉ የነበረው ኮሚሽን ሙሉ በሙሉ ተነስቷል ፡፡ 2. የብድር መመለሻ የመክፈያ ጊዜ ደንበኞቻችን እንዲራዘምላቸው ለሚያቀርቡት ጥያቄ ይከፈል የነበረው ኮሚሽን ሙሉ በሙሉ ተነስቷል ፡፡ 3. ደንበኞቻችን ከኤቲኤም ገንዘብ ሲያወጡ ይከፍሉ የነበረውን የኮሚሽን ክፍያ ተነስቶ ነጻ ሆኗል ፡፡
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል…
•በርካታ ሰዎች ሊገኙባቸው በሚችሉ መሰብሰቢያ ቦታዎች ላይ የምናሳልፈውን ጊዜ ማስቀረት •እጅን በንጹህ ውሃና ሳሙና አዘውትሮ መታጠብ •ከሰዎችጋር አለመጨባበጥ •አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ ከሌሎች ሰዎች ጋር የሚኖርን አላስፈላጊ ንክኪን እናስወግድ፡፡ •ሳል ወይም ትኩሳት ካለው ግለሰብ ቢያንስ ሁለት እርምጃ ርቀት ያህል መራቅ •እጅን በአግባቡ ሳይታጠቡ አይንና አፍንጫን አለመንካት •በሚያነጥሱበት እና በሚያስሉበት ጊዜ አፍና አፍንጫን በሶፍት ወይም ክርንን አጥፈው […]
Awash Bank with the aim of easing burdens on businesses due to the COVID- 19 spread
Awash Bank with the aim of easing burdens on businesses due to the COVID- 19 spread, waives the commission fee paid to extend Letters of Credit, rescheduling of loans and ATM withdrawal fees effective April 1 st, 2020.
አዋሽ ባንክ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ የብር አስር ሚሊየን /10,000,000.00 / ድጋፍ ለብሔራዊው የኮቪድ-19 የድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ለግሷል፡፡
Awash Bank inaugurated the full-fledged interest free branch #Barakaa Branch in Shashemene town on March 07, 2020.
አዋሽ ባንክ የካቲት 27 ቀን 2012 ዓ.ም ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት፣ በሐላባ ከተማ ‘አማና’ ተብሎ የተሰየመውን የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት አድረጓል፡፡
በመላው የአገሪቱ ክፍሎች ለደንበኞቹ ቀልጣፋ፣ የተሟላና ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በመስጠት የሚታወቀው ባንካችን አገልግሎቱን በተሻለ ደረጃ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን እስከ ዛሬ ድረስ በሁሉም ቅርንጫፎች በመስኮት ደረጃ ይሰጥ የነበረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልገሎትን አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን በመክፈት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሠረት ይህን ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ኢክኽላስ […]