አዋሽ ባንክ የካቲት 27 ቀን 2012 ዓ.ም ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ በደቡብ ብሔሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት፣ በሐላባ ከተማ ‘አማና’ ተብሎ የተሰየመውን የተሟላ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጥ ቅርንጫፍ አስመርቆ ለአገልግሎት ክፍት አድረጓል፡፡

በመላው የአገሪቱ ክፍሎች ለደንበኞቹ ቀልጣፋ፣ የተሟላና ዘመናዊ የባንክ አገልግሎት በመስጠት የሚታወቀው ባንካችን አገልግሎቱን በተሻለ ደረጃ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን እስከ ዛሬ ድረስ በሁሉም ቅርንጫፎች በመስኮት ደረጃ ይሰጥ የነበረውን ከወለድ ነፃ የባንክ አገልገሎትን አሁን ደግሞ ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ ቅርንጫፎችን በመክፈት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ መሠረት ይህን ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ኢክኽላስ ብሎ በመሰየም (ብራንድ በማድረግ) እንቅስቃሴ የጀመረ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወለድ ነፃ የባንክ አገለግሎት ብቻ የሚሰጡ በአዲስ አበባ ከተማ አራት ቅርንጫፎች፣ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን መልካ ራፉ ከተማ፣ በጅግጅጋ እና በጅማ ከተማ በመክፈት የተሟላ የባንክ አገለግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡

Share
Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram

Apr 25, 2024 EXCHANGE Rate
Currency Buying Selling
USD
56.8795 58.0171
GBP
67.5577 68.9089
EUR
60.7928 62.0087
AED
14.0132 14.2935
SAR
13.7240 13.9985
CHF
59.3920 60.5798

Exchange Rate
Close